ጄፒ ጨርቃጨርቅ ኢትዮጵያ
Key Buyers: PVH
Country: Ethiopia
Last updated: 2018
ጄፒ ጨርቃጨርቅ ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ.ማ. (“ጄፒ”) የሚገኘው በሐዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ በትንሿ የደቡብዏ ከተማ ሐዋሳ ውስጥ ነው። በ40,000 ሜትር ስኩዌር ላይ የሚገኘው ጄፒ (ኢትዮጵያ) ጨርቃጨርቅ ኩባንያ፣ በቻይና፣ ባንግላዲሽ፣ ካምቦዲያ እና ቬየትናም ፋብሪካዎች ያሉት የቻይናው ኮንግላምሬት የውዢ ጂንማኦ ድርጅት አካል ነው፡፡ ፋብሪካው የዞኑ ብቸኛ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካን እንዲሁም የጥጥ ሸሚዞችን የሚያመርት የልብስ ማምረቻ ተቋሞችን ያጠቃልላል ይህም የሰራተኛ መብቶች ጥምረት የምርምር ርዕሰ ጉዳይ ነበር። ውዢ ጂንማኦ በ2019 ዓ.ም በፋብሪካው ከ2,500 እስከ 3,000 ሰራተኞችን ለመቅጠር በእቅድ ማስቀመጡ ተዘግቧል። የልብስ ተቋሙ በአሁኑ ጊዜ ለፒቪኤች ያመርታል። የጨርቃጨርቅ ፋብሪካው በዞኑ ውስጥ ላሉ ፋብሪካዎች የጨርቃጨርቅ ምርት እንደሚያቀርብ ይታወቃል።
የሰራተኛ መብቶች ጥምረት ሪፖርት በሚከተሉት ጉዳዮች ዙሪያ ጥሰቶችን አግኝቷል፡
- ደሞዝ እና ሰአታት
- የቅጥር ውል አለመስጠት
- የቅጣት ደመወዝ ቅነሳ/ያልተከፈለ የጉልበት ሥራ
- የክፍያ ሰነዶችን አለመስጠት
- ያልተቆራረጠ የምግብ መመገቢያ ጊዜ አለመስጠት
- በነፍሰ ጡር ሰራተኞች ላይ የሚደረግ መድልዎ
- ትንኮሳ እና ጥቃት
- የቃላት ጥቃት
Read More:
Join our newsletter
Sign up to the WRC’s mailing list to stay updated on our work.