ኤምኤኤ አልባሳትና ጨርቃጨርቅ፣ ከብር ኢንተርፕራይዞች
Key Buyers: Asda, Bonghwa, DVH Apparel, Edwards, H&M, MOC, Obermeyer, Trimark Sportswear, Walmart
Country: Ethiopia
Last updated: 2018
በትግራይ ሰሜናዊ አውራጃ በመቀሌ ከተማ የተመሰረተው ኤምኤኤ አልባሳት እና ጨርቃጨርቅ (ኤምኤኤ) እንደ አውሮፓ አቆጣጠር 2016 ዓ.ም ላይ 1600 ሰራተኞች ቀጥሮ ያሰራ ነበር፡፡ በኢትዮጵ ውስጥ ከታች ወደ ላይ ከተዋቀሩት 17ቱ ፋብሪካዎች አንዱ የሆነው እና ባቤትነቱ የኢትዮጵያዊ ባለሀብት የሆነው ይህ ፋብሪካ የጥጥ ምርቶችን የመፍተል እና የመሸመን እንዲሁም ልብሶችን የመገጣጠም (መቁረጥ፤ መስራት እና መስፋት) አቅም ያለው ነው፡፡ የሚያመርታቸውም ምርቶች ሱሪዎችን፣ የውስጥ ሱሪዎችን፣ ሸሚዞች፣ ቲሸርቶችን እና የቤት ውስጥ ጨርቃ ጨርቅን ያጠቃልላል።
የሰራተኛ መብቶች ጥምረት ሪፖርት በሚከተሉት ጉዳዮች ዙሪያ ጥሰቶችን አግኝቷል፡-
- ደሞዝ እና ሰአታት
- የቅጣት ደመወዝ ቅነሳ/ያልተከፈለ የጉልበት ሥራ
- አስገዳጅ የትርፍ ሰዓት ስራ
- ያልተከፈለ የትርፍ ሰዓት እና መሰረት የሌላቸው የክፍያ ልማዶች
- በመመገቢያ ሰዓት ስራ ማሰራት
- ትንኮሳ እና ጥቃት
- ወሲባዊ ትንኮሳ
- ከእርግዝና ጋር የተያያዘ ትንኮሳ
- የቃላት ጥቃት
- የስራ ጤና እና ደህንነት
- ሠራተኞች በሥራ ወቅት መውደቅ
- ውስን የመጠጥ ውሃ አቅርቦት
- ውስን የመጸዳጃ ቤት አገልግሎት
Read More:
Join our newsletter
Sign up to the WRC’s mailing list to stay updated on our work.